Kolfe Prosperity Party Inspection And Ethics Commission

Kolfe Prosperity Party Inspection And Ethics Commission Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Kolfe Prosperity Party Inspection And Ethics Commission, Men's clothes shop, addis ababa, Addis Ababa.

 #ጠንካራ ኢንስፔክሽን ለጠንካራ ፖርቲ!!በኮ/ቀ/ክ/ከተማ የብልጽግና ኢንስፔክሽን ስነ ምግባር ኮሚሽን ቅ/ጽ/ቤት  የዘጠኝ ወር የስራ አፈፃፀም   ውይይት ተደረገ!!ግንቦት 7/2018 ዓ/ም ...
15/05/2026

#ጠንካራ ኢንስፔክሽን ለጠንካራ ፖርቲ!!

በኮ/ቀ/ክ/ከተማ የብልጽግና ኢንስፔክሽን ስነ ምግባር ኮሚሽን ቅ/ጽ/ቤት የዘጠኝ ወር የስራ አፈፃፀም ውይይት ተደረገ!!
ግንቦት 7/2018 ዓ/ም ኮ/ክ/ከተማ የብልጽግና ኢ/ስ/ኮ/ቅ/ጽ/ቤት

በብልፅግና ፓርቲ ኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ኢንስፔክሽን እና ሥነ-ምግባር ኮሚሽን ቅ/ጽ/ቤት የዘጠኝ ወር የስራ አፈጻጸም የክፍለ የወረዳዎች ኮሚሸን አመራሮች፣ በተገኙበት ውይይት አካሄደ።

በክፍለ ከተማው የሚገኙ የ11ዱም ወረዳዎች ሪፖርት መነሻ ያደረገ ውይይት የተደረገበት ሲሆን በ2018 ዓ.ም የ3ኛ ሩብ ዓመት የዝግጅት ምዕራፍ ስራዎች ማለትም የውስጠ ፓርቲ ዴሞክራሲን ማጎልበት ፣ በመተዳደሪያ ደንቡና በመመርያዎች ጠብቆ የአባላት መልሶ ማደራጀት ፣ የአባል ምልመላ ጥራትን ማረጋገጥ ፣ እንዲሁም ጠንካራ ተቋማት ከመፍጠርና አባላትን ከማጠናከር አንፃር የተሰሩ ስራዎችን እንዲሁም የ2018 ዓ/ም ሀገራዊ ምርጫ ያለንበትን እና የቀጣይ አቅጣጫ ጥልቅ ውይይት አካሄዷል ።

በቀጣይም ቀሪ ተግባራት ርብርብ የሚሹ ጉዳዬች ላይ ትኩረት ማድረግ ያስፈልጋል ተብሏል።

በብልፅግና ፓርቲ የምርጫ አሰራርና ስነ-ምግባር መመሪያ ላይ ለህብረትና ቤተሰብ ሰብሳቢዎች ስልጠና ተሰጠ።የኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ የብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ከኢንስፔክሽንና ስ...
12/05/2026

በብልፅግና ፓርቲ የምርጫ አሰራርና ስነ-ምግባር መመሪያ ላይ ለህብረትና ቤተሰብ ሰብሳቢዎች ስልጠና ተሰጠ።

የኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ የብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ከኢንስፔክሽንና ስነ-ምግባር ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት ጋር በመተባበር በፓርቲው የምርጫ አሰራር ስርዓት (ስነ-ምግባር) መመሪያ ላይ ያተኮረ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ለህብረት እና ለቤተሰብ ሰብሳቢዎች ዛሬ ሰጥቷል።

የክፍለ ከተማው የብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ አሚ ሙሄ አሊ ስልጠናውን በንግግር የከፈቱ ሲሆን ፓርቲው የጀመረውን የሪፎርም ጉዞ ለማሳካት ግልጽነትና ተጠያቂነት ያለው የምርጫ አሰራር መከተል አማራጭ የሌለው ጉዳይ መሆኑን ገልጸዋል።

አቶ አሚ አክለውም ማንኛውም የፓርቲው መዋቅርና አባል የፓርቲውን የውስጥ ዲሞክራሲ በሚያጠናክር መልኩ የምርጫ ስነ-ምግባር መመሪያውን በአግባቡ መተግበር እንደሚገባውም አንስተዋል።

የህብረትና የቤተሰብ ሰብሳቢዎች ከመመሪያው ባሻገር በዲሞክራሲያዊ ባህል ግንባታ ላይ ለሌሎች አባላት አርአያ መሆን እንዳለባቸውም ጠቁመዋል።

የክፍለ ከተማው የብልፅግና ፓርቲ የፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ኢብራሒም መሀመድ በበኩላቸው መመሪያውን እስከ ታችኛው የፓርቲ መዋቅር የማውረድ ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸዋል።

ኃላፊው አክለው ሰላምና ዲሞክራሲ የሚረጋገጠው በህዝብ ንቁ ተሳትፎ ነው ያሉ ሲሆን፣ መጪው ሀገር አቀፍ ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊ፣ ዲሞክራሲያዊ እና ተአማኒ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የብልፅግና ህብረትና ቤተሰብ አደረጃጀቶች ያላቸውን ሚና አጠናክረው እንዲቀጥሉ ጥሪ አቅርበዋል።

በመጨረሻም ሰልጣኞቹ በመመሪያው ዙሪያ ሰፊ ውይይት ያደረጉ ሲሆን ለቀጣይ ስራዎች ዝግጁ መሆናቸውን አረጋግጠዋል።

 #ጠንካራ ኢንስፔክሽን ለጠንካራ ፖርቲ !!‎የመልካም ልምድ ልውውጥ ስኬታማ አፈፃፀሞችን ለማስቀጠል እና ወሳኝና ቁልፍ ተግባር ነው ። ‎‎   ግንቦት 03/2018 ዓ ም ኮ/ቀ/ክ/ከተማ የኢ/...
11/05/2026

#ጠንካራ ኢንስፔክሽን ለጠንካራ ፖርቲ !!
‎የመልካም ልምድ ልውውጥ ስኬታማ አፈፃፀሞችን ለማስቀጠል እና ወሳኝና ቁልፍ ተግባር ነው ።

‎ ግንቦት 03/2018 ዓ ም ኮ/ቀ/ክ/ከተማ የኢ/ስ/ኮ/ቅ/ጽ/ቤት
‎የአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ የብልጽግና ኢንስፔክሽንና ስነ ምግባር ኮሚሽን ቅ/ፅ/ቤት ወደ ኮልፌ ክ/ከተማ የብልጽግና ኢ/ስ/ኮሚሽን ቅ/ጽ/ቤት በመምጣት የኮሚሽን አመራሮች በተገኙበት የልምድ ልውውጥ ተካሔደ።
‎ ለልምድ ልውውጡ የተዘጋጁ ሰነዶች የተሞክሮ ቅመራ ሰነድ በክፍለከተማው የዘርፍ ጽ/ቤት ኃላፊ በወይዘሮ ሉባባ አደም እ የቀረበ ሲሆን ቴክኖሎጂ የማበልጸግና ቴክኖሎጂው አጠቃላይ የመረጃ ማዘመን ተግባር በአቶ ደረጀ ፍቃዱ ቀርቦ ውይይት ተደረገበት።
‎በቁርጠኛ የአመራር ሰጪነት የተጠኑ ውጤትን በተሻለ መልኩ ለማስቀጠል መሰረታዊ ለውጥ የሚያመጣው የልምድ ልውውጥ በክፍለከተማችን ኮሚሽን መደረጉ በስኬት ያከናወናቸውን ውጤታማ ተግባራትን በዝርዝር ከእቅድ ዝግጅት ጀምሮ ውጤትን ተቋማዊ ለማድረግ በሚያስችል መልኩ እየተከናወነ በመሄዱ ባለፊው የዘጠኝ ወር የስራ አፈፃፀም በታላቅ ስኬት ማጠናቀቅ መቻሉን በተቋሙ አቶ በያን ገመዱ ተገልጿል ።

‎በመድረኩ የተገኙት የወረዳው ብልፅግና የኢንስፔክሽንና ስነ ምግባር ኮሚሽን አመራሮች የተደረገው የልምድ ልውውጥ ለእያንዳንዱ ተቋማት የተሞክሮ ማዕከል ሊሆኑ እንደሚችሉ 24/7 በመትጋት የተገኘውን ወሳኝ ውጤትን ለሌሎች በማካፈል እንደ የተሞክሮ ማዕከል ለመሆን እንሰራለን ሲሉ አቃቂ ቃሊቲ ክ/ከተማ የብ/ኢ/ስ/ኮሚሽን ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ፈይሳ ከባሺ ገልፀዋል ።
‎ለልምድ ልውውጡ የተገኙት የኮሚሽኑ የወረዳ አመራሮች በበኩላቸው ሁሌም የተሻለ አፈፃፀም ያስመዘገቡ ተቋማትን ልምድና አሰራርን እንደ መነሻ በመጠቀም በቀጣይ ለእያንዳንዱ ተግባር ተደማሪ አቅም ይሆናል በማለት ገልፀዋል። ውጤታማ የተቋም መረጃ አያያዝና የሰራተኞች ቁርጠኝነት እንዲሁም የአመራር ሰጪነት በኮሚሽኑ አጠቃላይ ስራዎችበቂ ልምድ መቅሰማቸውን ጠቅሰዋል ።

በየደረጃው የሚገኙ የብልጽግና ኢንስፔክሽን እና ስነ-ምግባር ኮሚሽን መዋቅሮች ጥንካሬ ለፓርቲያችን ጥንካሬ ወሳኝ አቅሞች ናቸው ! በብልፅግና ኢንስፔክሽን እና ስነ-ምግባር ኮሚሽን የአዲስ አበ...
06/05/2026

በየደረጃው የሚገኙ የብልጽግና ኢንስፔክሽን እና ስነ-ምግባር ኮሚሽን መዋቅሮች ጥንካሬ ለፓርቲያችን ጥንካሬ ወሳኝ አቅሞች ናቸው !

በብልፅግና ኢንስፔክሽን እና ስነ-ምግባር ኮሚሽን የአዲስ አበባ ቅ/ፅ/ቤት ከተማ እስከ ወረዳ ያሉ ኮሚሽን አመራሮች የኮሚሽኑን የ2018 ዓ.ም የአሰር ወራት አፈፃፀም በመገምገም ጥንካሬዎችን ለማስቀጠል፣ ጉድለቶችን ለማረም በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ ተግባቦት ፈጠሩ፡፡

በብልፅግና ኢንስፔክሽን እና ስነ-ምግባር ኮሚሽን የአዲስ አበባ ቅ/ፅ/ቤት ኃላፊ ወ/ሮ መሪማ ደሊል በውይይቱ ላይ እንደተናገሩት በዝግጅት ምዕራፉ መሰረታዊ ስራዎችን በማከናወን ወደ ተግባር በመገባቱ ባለፉት አስር ወራት ኮሚሽኑ አበረታች ውጤቶችን ማስመዝገቡን ገልፀዋል።

የየካ ክፍለ-ከተማ በብልፅግና ፓርቲ ቅ/ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ መገርሳ ገላና የኮሚሽኑ ሚና አሰራርን ማስጠበቅ በመሆኑ ተግባራት በፓርቲያችን መተዳደሪያ ደንብ እና መመሪያዎች መሰረት መከናወናቸውን በየደረጃው ያለው ኮሚሽን ኢንስፔክሽን በመስራት እና ግብረ-መልስ በመስጠት ለፓርቲ መጠናከር የራሱን ሚና እየተወጣ ያለ ተቋም መሆኑን በመግለጽ በየደረጃው የሚገኘው አመራር ፓርቲውን የማጠናከር ሚናውን አጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ አስረድተዋል።

በብልፅግና ኢንስፔክሽን እና ስነ-ምግባር ኮሚሽን የአዲስ አበባ ቅ/ፅ/ቤት ምክትል ኃላፊ የሆኑት አቶ አታላይ ምህረት እና አቶ ጉዲሳ ገቢሳ የአስር ወራት ሪፖርት እና የአስር ወራት የክ/ከተሞች የሪፖርት ግብረ-መለስ በተከታታይ በማቅረብ በተሳታፊዎች ውይይት ተደርጓል፡፡

የፓርቲያችን የውስጠ-ፓርቲ ጤንነትን ለማስጠበቅ የተለያዩ የአቅም ግንባታ እና የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠናዎችን በመስጠት የብልፅግና ፓርቲ መተዳደሪያ ደንብ እና መመሪያዎች እንዲታወቁና እንዲከበሩ አበረታች ስራዎች መከናወናቸው በውይይቱ ተጠቅሷል።

የብልፅግና ኢንስፔክሽን እና ስነ-ምግባር ኮሚሽን አዲስ አበባ ቅ/ጽ/ቤት በ4ኛ ሩብ አመት መከናወን የሚገባቸው ተግባራት ቼክ-ሊስት የቀረበ ሲሆን በአመቱ አቅደን ያላጠናቀቅናቸው ተግባራትን በመለየት በዚህኛው ሩብ አመት ማጠናቀቅ እንደሚገባ አቅጣጫ ተሰጥቷል፡፡

“ጠንካራ ኢንስፔክሽን ለጠንካራ ፓርቲ”

  "ኢትዮጵያ ወደ ተምሳሌት ሀገር!" በሚል መሪ ቃል ከብልፅግና ህብረት ጀምሮ በ11ዱም ወረዳዎች ሲካሄድ የነበረው የ2018 በጀት አመት የ3ኛ ሩብ አመት የብልፅግና ፓርቲ ኮንፈረንስ የማጠቃ...
07/04/2026



"ኢትዮጵያ ወደ ተምሳሌት ሀገር!" በሚል መሪ ቃል ከብልፅግና ህብረት ጀምሮ በ11ዱም ወረዳዎች ሲካሄድ የነበረው የ2018 በጀት አመት የ3ኛ ሩብ አመት የብልፅግና ፓርቲ ኮንፈረንስ የማጠቃለያ መድረክ በኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ተካሄደ።

በኮንፈረንሱ ላይ አቶ አሚ ሙሄ የኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ፤ አቶ አከበረኸኝ ወጋገን የኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ምክትል ስራ አስፈፃሚና የሥራና ክህሎት ጽ/ቤት ኃላፊ፤ አቶ በያን ገመዱ የኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ብልፅግና ኢንስፔክሽንና ሥነ-ምግባር ኮሚሽን ቅ/ፅ/ቤት ኃላፊ፤ የክፍለከተማ እና የወረዳ አመራሮች ፤ በድምፅ የሚሳተፉ አባላት እና ጥሪ የተደረገላቸው ተጋበዥ እንግዶች ተገኝተዋል።

በመድረኩም የኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ፅ/ቤት እንዲሁም የኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ብልፅግና ኢንስፔክሽንና ሥነ-ምግባር ኮሚሽን ቅ/ፅ/ቤት የ9 ወራት ዕቅድ አፈፃፀም ለኮንፈረንሰኛው ቀርቦ ሰፊ ውይይት ከተደረገ በኋላ ፀድቋል።

በኮንፈረንሱ ላይ በመገኘት መልዕክት ያስተላለፉት የክፍለ ከተማው ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ አሚ ሙሄ በበኩላቸው በበጀት አመቱ ታቅደው የተፈፀሙ መደበኛ የውስጠ ፓርቲ ተግባራት እንዳሉ ገልፀው ጉደለት የታየባቸውን ፈጥኖ ለማረም እርብርብ ያስፈልጋል ብለዋል ፤ በተጨማራም የ7ኛው ሀገራዊ ምርጫ በፓርቲያችን አሸናፊነት ለማጠናቀቅ መላው አመራር እና አባል የፓርቲያችንን ብሎም የሀገሪቱን የምርጫ ህጎች አክብሮ መንቀሳቀስ እንዲሁም ሁሉም የፓርቲ አደረጃጀቶች ወደተሟላ ስምሪት መግባት እንደሚገባቸው በአንክሮ ገልፀዋል።

አክለውም ኮንፈረንስ የፓርቲያችን ወሳኝ ተግባር መሆኑን ገልፀው መድረኩን ከመደበኛ ክዋኔ በተጨማሪ ለአሁናዊ የምርጫ ስራዎቻችን ተደማሪ አቅም አድርጉ መጠቀም ይገባል ብለዋል።

የክፍለ ከተማው ብልፅግና ኢንስፔክሽንና ሥነ-ምግባር ኮሚሽን ቅ/ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ በያን ገመዱ በበኩላቸው ለፀና ሰላም ምህዳሩ ለሰፋ ዲሞክራሲ እንዲሁም ሁለተናዊ ብልፅግና እውን መሆን ለምትሻ ሀገር የአንድ ፓርቲ አባል ተሳትፎ ወሳኝ በመሆኑ ብልፅግና ከአመት አመት እያስመዘገበ ለመጣው ለውጥና ለተቋም ግንባታ መጠናከር ጉልህ ሚና ያለው በፓርቲው አሰራርና አደረጃጀት መመሪያ መሰረት በየሩብ አመቱ የሚካሄደው የኮንፈረንስ መድረክ መሆኑን በመግለፅ በዚህ አመት በሚካሄደው 7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ላይ አባላችን የምርጫ ህጉንና ዲሲፕሊኑን አክብሮ ሚናውን መወጣት አለበት ብለዋል።

በመድረኩ ከቀረቡ ሪፖርቶች መነሻነት የተነሱ ሀሳቦች ላይ ማብራሪያ እና ምላሽ በመስጠት ኮንፈረንሱ ተጠናቆል።

 #ጠንካራ ኢንስፔክሽን ለጠንካራ ፖርቲ!!በኮ/ቀ/ክ/ከተማ የብልጽግና ኢንስፔክሽንና ስነ-ምግባር ኮሚሽን ቅ/ጽ/ቤት የቅድመ ኮንፈረንስ ዝግጅት ከፖርቲ ጋር የጋራ ተደርጓል!!መጋቢት 17/201...
26/03/2026

#ጠንካራ ኢንስፔክሽን ለጠንካራ ፖርቲ!!
በኮ/ቀ/ክ/ከተማ የብልጽግና ኢንስፔክሽንና ስነ-ምግባር ኮሚሽን ቅ/ጽ/ቤት የቅድመ ኮንፈረንስ ዝግጅት ከፖርቲ ጋር የጋራ ተደርጓል!!

መጋቢት 17/2018 ዓ/ም

በኮ/ቀ/ክ/ከተማ የብልጽግና ኢንስፔክሽንና ስነ-ምግባር ኮሚሽን ቅ/ጽ/ቤት የ2018 ዓ/ም የ3ተኛ ሩብ አመት የቅድመ ኮንፈረንስ ዝግጅት ከፖርቲ ጋር የጋራ ተደርጓል!!

የመሰፈፀሚያ እቅድ በአቶ አደም መሀመድ የቀረበ ሲሆን ዋናው አላማው ከዚህ በፊት የነበሩት የኢንስፔክሽን ክፍተት ሊያርም የሚችል እና በቀጣይ አባላት ተልእኮ የሚወስዱበት መደርክ በመሆኑ ከፖርቲ ጋር በጋራ መሰራት እንዳለበት ገልጸዋል።

የክ/ከተማው የብልጸግና ኢ/ስ/ኮሚሽን ቅ/ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ በያን ገመዱ እንዳሉት ኮንፈረንስ የአባላት የአቅም ግንባታ መድረክ እንደመሆኑ መጠን በጥብቅ ዲስፕሊን መፈፀም እንዳለበት አሳስበዋል።

በመጨረሻም የክ/ከተማው የብልጸግና ኢ/ስ/ኮሚሽን ቅ/ጽ/ቤት ም/ል ሃላፊ የሆኑት ወ/ሮ ሉባባ አደም አክለው እንደገለፁት:ኮንፈረንሱ መላ አባላችን የምናሳትፍበት በመሆኑ ቅድመ ዝግጅት ላይ ትኩረት መደረግ አለበት ብለዋል።

 #ጠንካራ ኢንስፔክሽን ለጠንካራ ፖርቲ!!የውስጠ ፓርቲ ስራዎችን ለማጠናከር እና ጠንካራ ተቋም ለመፍጠር የኢንፔክሽን  ስራዎች ሚናቸው ከፍተኛ ነው!!!መጋቢት 10/2018 ዓ/ም ኮ/ቀ/ክ/ከተ...
19/03/2026

#ጠንካራ ኢንስፔክሽን ለጠንካራ ፖርቲ!!
የውስጠ ፓርቲ ስራዎችን ለማጠናከር እና ጠንካራ ተቋም ለመፍጠር የኢንፔክሽን ስራዎች ሚናቸው ከፍተኛ ነው!!!

መጋቢት 10/2018 ዓ/ም ኮ/ቀ/ክ/ከተማ የብልጽግና ኢ/ስ/ኮሚሽን ቅ/ጽ/ቤት

የኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ኢንስፔክሽን እና ሥነ-ምግባር ኮሚሽን ቅ/ጽ/ቤት የተቋቋመው የኢንስፔክሽን ቡድን በየወረዳው ያካሄደውን የ2018 ዓ.ም የ3ኛ ሩብ ዓመት የፐርፎርማንስ ኦዲት ኢንስፔክሽን ግኝት ላይ የክፍለ ከተማና የወረዳዎች ፓርቲ ኮሚቴዎች በተገኙበት በዛሬው እለት ውይይት አካሄደ።

የፐሪፎርማንስ የኦዲት ሪፖርት የክ/ከተማው ብልፅግና ኢንስፔክሽን ቅ/ጽ/ቤት ም/ል ሃላፊ በሆኑት ወ/ሮ ሉባባ አደም የቀረበ ሲሆን: የኢንፔክሽን ቡድኑ በክፍለ ከተማው ዘጠኝ ወረዳዎች በ2018 ዓ.ም የ3ኛ ሩብ ዓመት የዝግጅት ምዕራፍ ስራዎች ማለትም የውስጠ ፓርቲ ዴሞክራሲን ማጎልበት ፣ በመተዳደሪያ ደንቡና በመመርያዎች ጠብቆ የአባላት መልሶ ማደራጀት ፣ የአባል ምልመላ ጥራትን ማረጋገጥ ፣ እንዲሁም ጠንካራ ተቋማት ከመፍጠርና አባላትን ከማጠናከር አንፃር የተሰሩ ስራዎችን ባካሄደው የኢንስፔክሽን ግብረ መልስ ጥልቅ ውይይት ቀርቧል ።

በብልፅግና ፓርቲ የኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ቅ/ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ አሚ ሙሄ በመድረኩ ኮሚሽኑ ያካሄደው ኢንስፔክሽን በ3ኛ ሩብ አመት አፈፃፀም ያስመዘገብናቸውን ጠንካራ ጎኖች የበለጠ ለማስቀጠል በድክመት የለየናቸውን ለማረም እና ለፖርቲው እሴት ሊጨምር የሚችል ተግባራትን ለመፈጸም መልካም አጋጣሚ እንደሆነ ጠቅሰዋል።

‎አያይዘውም የያዝነው በጀት አመት ድርብ ተልእኮ ያለበት ወቅት በመሆኑ የኮሚሽኑ መዋቅር መመሪያዎችንና አሰራሮችን በማክበርና በማሰከበር በኩል ከወትሮው ለየት ባለ አግባብ ተግቶ መስራት እንደሚገባውም አሳስበዋል። በተለይ በታችኛው መዋቅሮች የሚታየው ክፍተቶች በማረም "ጠንካራ ኢንስፔክሽን ፤ ለጠንካራ ፓርቲ" የሚለውን መሪ ቃል ተግባራዊነት በየደረጃው የሚገኘውን የኮሚሽን መዋቅሮች ሚናቸውን በሚገባ እንዲወጡ ማድረግ መስራት እንደሚገባ አስታውቀዋል።

የኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ የኢስፔክሽንና ስነምግባር ኮሚሽን ቅ/ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ በያን ገመዱ በኮሚሽኑ በተደረገው ኢንስፔክሽን ጠንካራ ኢንስፔክሽን ለጠንካራ ፓርቲ የሚለውን መርህ መሠረት በማድረግ የፓርቲው ፕሮግራምና መተዳደሪያ ደንብና የኢንስፔክሽን ስነምግባር ኮሚሽኑን መመሪያን ተፈፃሚነቱን በማረጋገጥ ፓርቲው እንዲጠናከር እየተሰሩ ያሉት የኢንስፔክሽን ተግባራት ተጠናክረዉ ሊቀጥሉ እንደሚገባ ገልፀው በቀሪ ጊዜያት ትኩረት ሊደረግባቸው የሚገቡ ተግባራትን መለየት እና በክፍተት የሚታዩ ጉዳዮች ፈጥኖ እንዲታረሙ ማድረግ እንደሚገባ አሳስበዋል።

የኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ብልጽግና ፖርቲ ድርጅት ዘርፍ ሀላፊ የሆኑት አቶ ወርቅነህ ሞርካ በበኩላቸው ኮሚሽኑ የፓርቲያችን የፖለቲካ ጤንነት እንዲጠበቅ ፣ የአባላት መብትም እንዲረጋገጥ የተጣለበትን ኃላፊነት ለመወጣት ብርቱ ጥረት እያደረገ መሆኑን ጠቅሰው። አሰራር ተግባራዊ እንዲደረግ እንዲሁም በኮሚሽኑ በተካሄደው ኢንስፔክሽን ግኝት ለማረም ሁሉም ወረዳ የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።

በኮሚሸኑ በኩል ጠንካራ የክትትልና የድጋፍ ብሎም የቁጥጥር ስራዎችን አጠናክሮ ማስቀጠል አሰፈላጊ በመሆኑ በየደረጃው የሚገኝ የኮሚሸን አመራሮችና ኮሚቴዎች ውጤታማ ስራዎች እንዲፈጽሙ በመድረኩ ተገልፆል።

"ጠንካራ ኢንስፔክሽን ለጠንካራ ፓርቲ ! "

 #ጠንካራ ኢንስፔክሽን ለጠንካራ ፖርቲ!!በኮ/ቀ/ክ/ከተማ የብልጽግና ኢንስፔክሽን ስነ -ምግባር ኮሚሽን ቅ/ጽ/ቤት  የዘጠኝ ወር የስራ አፈፃፀም መነሻ ያደረገ የፐሪፎርማንስ ኦዲት ውይይት ተ...
16/03/2026

#ጠንካራ ኢንስፔክሽን ለጠንካራ ፖርቲ!!

በኮ/ቀ/ክ/ከተማ የብልጽግና ኢንስፔክሽን ስነ -ምግባር ኮሚሽን ቅ/ጽ/ቤት የዘጠኝ ወር የስራ አፈፃፀም መነሻ ያደረገ የፐሪፎርማንስ ኦዲት ውይይት ተደረገ!!
መጋቢት 7/2018 ዓ/ም ኮ/ክ/ከተማ የብልጽግና ኢ/ስ/ኮ/ቅ/ጽ/ቤት

በብልፅግና ፓርቲ ኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ቅ/ፅ/ቤት ኢንስፔክሽን እና ሥነ-ምግባር ኮሚሽን የተቋቋመው የኢንስፔክሽን ቡድን በየወረዳው ያካሄደውን የ2018 ዓ.ም የዘጠኝ ወር የፐርፎርማንስ ኦዲት የኢንስፔክሽን ግኝት ላይ የክፍለ ከተማና የወረዳዎች ኮሚሸን ኮሚቴዎች፣ እንዲሁም ፓርቲ ተወካዬች በተገኙበት ውይይት አካሄደ።

የኢንስፔክሽን ቡድኑ በክፍለ ከተማው የሚገኙ የ9ኙም ወረዳዎች የብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ /ቤት በ2018 ዓ.ም የ3ኛ ሩብ ዓመት የዝግጅት ምዕራፍ ስራዎች ማለትም የውስጠ ፓርቲ ዴሞክራሲን ማጎልበት ፣ በመተዳደሪያ ደንቡና በመመርያዎች ጠብቆ የአባላት መልሶ ማደራጀት ፣ የአባል ምልመላ ጥራትን ማረጋገጥ ፣ እንዲሁም ጠንካራ ተቋማት ከመፍጠርና አባላትን ከማጠናከር አንፃር የተሰሩ ስራዎችን ባካሄደው የኢንስፔክሽን ግብረ መልስ ጥልቅ ውይይት አካሄዷል ።

በቀጣይም የክ/ከተማው እና የወረዳ የፖርቲ ኮሚቴ አመራሮች በተገኙበት የጋራ እንደሚደረግ በውይይቱ ተገልጿል!!

 #ጠንካራ ኢንስፔክሽን ለጠንካራ ፓርቲ ‼የኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ኢንስፔክሽን እና ስነምግባር ኮሚሽን በኮ/ቀ/ክ/ከተማ በ9 ወረዳዎች የዘጠኝ  ወር የፕሪፎርማስ ኦዲት ኢንስፔክሽን ምልከታ...
11/03/2026

#ጠንካራ ኢንስፔክሽን ለጠንካራ ፓርቲ ‼

የኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ኢንስፔክሽን እና ስነምግባር ኮሚሽን በኮ/ቀ/ክ/ከተማ በ9 ወረዳዎች የዘጠኝ ወር የፕሪፎርማስ ኦዲት ኢንስፔክሽን ምልከታ በማድረግ ላይ ይገኛል።

መጋቢት2/2018ዓ/ም ኮ/ቀ/ክ/ከተማ የብልጽግና ኢ/ስ/ኮ/ቅ/ጽ/ቤት

ጠንካራ ተቋም ለመፍጠር የኢንስፔክሽን ተግባራት ከፍተኛ ሚና ያለው ሲሆን በማንኛውም ተግባር ጠንካራ ፓርቲ ሲኖር ጠንካራ አባል፣የጠራ የተግባር አፈጻጸምና ጠንካራ ግንዛቤ በመያዝ ፖርቲን በማጠናከር እና በመገንባት የጎላ ድርሻ እንደሚኖረው የታመነበት ተግባር በመሆኑ :

የኢንስፔክሽኑ ዓላማም የ2018 በጀት ዓመት የዝግጅት እና የተግባር ምዕራፍ አፈጻጸም የፓርቲ ተቋም ግንባታ፣ የአደረጃጀትና የፖለቲካ ተግባራት ያሉበትን ደረጃ እና ሌሎች ዋና ዋና ነጥቦችን የሚዳስስ ሲሆን ጠንካራ ግብረመልስ እንደሚሰጡም ይጠበቃል።



Address

Addis Ababa
Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Kolfe Prosperity Party Inspection And Ethics Commission posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share