13/01/2024
በክቡር ጠቅላይ ሚንስትራችን ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ ሀሳብ አመንጪነትና ክትትል በሀገር ወዳድ ልበ-ቀና ባለሃብቶች ድጋፍ የተጀመረው የገበታ ለሀገር ንቅናቄ አካል የሆነው የወንጪ ሀይቅ ኤኮ ቱሪዝም መንደር ዛሬ በመመረቁ እንኳን ደስ አለን!
ያሉንን ሃብቶች በማየት አዕምሮ እና እጅን አቀናጅቶ በማልማት ከገበታ ለሸገር ጀምሮ በተለያዩ የሃገራችን ክፍሎች ከለውጡ በኃላ የተሰሩ ፕሮጀክቶች ለሃገራችን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ልማት እንደዚሁም የሃገር ገፅታ ግንባታ ትልቅ አስተዋፅዖ ያላቸው የቱሪስት መዳረሻ እየሆኑ ነው።
ይህ የወንጪ ሀይቅ ኤኮ ቱሪዝም መንደር እውን እንዲሆን ያስቻሉት ለክቡር ጠቅላይ ሚኒስትራችን፣ በፕሮጀክቱ ላይ የተሳተፉ፣ አስተዋፅዖ ያደረጉ ባለሃብቶቻችንን እና ያስተባበሩ አካላት ሁሉ ምስጋና ይገባቸዋል።