24/04/2026
ቁርአን ላይ ከተቀመጡ ታሪኮች ውስጥ ከሚገርሙኝ....የነብዩላህ ሙሳ love life!❤
ነብዩላህ ሙሳ, The big guy, the strong fit man፣ አንበሳው ከሀገራቸው አምባገነኑ የፊርአውንን መንግስት ሸሽተው ተሰደው ሲጓዙ መድየን ወደምትባል ቀበሌ ደረሱ። የቀበሌው ሰው ታዲያ መድየን ውስጥ ባለችዋ ብቸኛ የዉሀ ምንጭ እየተጋፋ ግመሉንና ፍየሉን ያጠጣል። ጉልበተኛ እዛ ነው የሚታየው በቃ። ያለችው ምንጭ አንድ ነች እዛ ተጋፍቶ የሚያጠጣውና ለራሱም የሚቀዳው አለ የተባለ ጠንካራ ወንድ ነው። የከተማው ወንድ ታዲያ ትግል የሚገጥመው እዛ ነው። ሁሉም ታግሎ ያጠጣል ይጠጣል። ከዛ ደካሞቹ ደግሞ ጉልበተኞቹ ታግለው አጠጥተው እስኪጨርሱ ዳር ላይ ተኮራምተው ይጠብቁና መጨረሻላይ በትግሉና በፍትጊያው የደፈረሰውን ውሀ እንስሳቶቻቸውንም ያጠጣሉ እነሱም ይጠጣሉ። ለቤታቸውም የደፈረሰውን ውሀ ይቀዳሉ። ታዲያ ምን ያርጉ💁
ነብዩላህ ሙሳ በስደት በረሀውን ተጉዘው መድየን ምንጭ ውሀ ሲደርሱ ሰዉ ይራኮታል። የጦፈ ትግል ነው ያለው። በዚ መሀል አሻግረው ሲያዩ ሁለት ሚስኪን ልጃገረዶች ጥግ ላይ ቆመው እንስሳቶቻቸውን ሰብሰብ አርገው ይጠብቃሉ። ሙሳ(አሰ) ሁኔታቸው ግራ ገባቸውና ተጠግተው ምነው እንስሳቶቻችሁን አታጠጡምን? ሲሉ ጠየቋቸው። እነሱም ምን እናርግ ብለህ ነው አቅም የለንም እዚ ተጋፍቶ ማጠጣት። አባታችንም ሽማግሌ ነው አቅም የለውም። ስለዚህ ጠብቀን ጉልቤዎቹ ሲጨርሱ እንጂ ማጠጣት አንችልም ሲሉ መለሱ። ሙሳም ነው እንዴ አሉና የልጆቹን ፍየሎች ይዘው ወደምንጩ በመሄድ ምንጩ ላይ ያለን ጉልቤ ሁሉ አተራመሱት። ለጉልቤም ጉልቤ አለው አሉ እትዬ ዙልፋ። ማን ይግፋቸው ሙሳን። እያንዳንዱን አሽቀንጥረው ጥለው የሴቶቹን ፍየሎች አጠጥተው ለራሳቸውም ጠጥተው ጉልቤውን ሁሉ ልክ አስገብተው ተመለሱና ፍየሎቹን ለሴቶቹ ሰተው ሂዱ በሉ ብለው እሳቸው ያው ስደተኛና ሙሳፊር ናቸውና መንገዳቸውን እስኪቀጥሉ ትንሽ ልረፍ ብለው ዛፍ ስር ቁጭ አሉ። ያላገቡ ላጤ የነበሩትና ስራም ቤትም መሄጂያም ማረፊያም ያልነበራቸው ስደተኛውና ሙሳፊሩ ነብዩላህ ሙሳ ዛፏ ስር ቁጭ ብለው َربِّ إِنِّي لِمَا أَنزَلْتَ إِلَيَّ مِنْ خَيْرٍ فَقِيرٌ" " ጌታዬ ሆይ እኔ አንተ ወደኔ ላወረድከው በጎ ነገር ከጃይ ነኝ" ሲሉ ዱአእ አደረጉ። እቺ ዱአእ ስንት ነገር መለሰች?እናየዋለን.... ግን እዚጋ ጀለሴ ለካ ከሴቶቹ አንደኛዋ እዛው wow ብላለች..ሁብ ጠብ አርጓታል። ሙሳ (አሰ) መች አወቁና
ሴቶቹ ቤታቸው እንደደረሱ በጊዜ መመለሳቸው ግራ የገባቸው አባታቸው ምነው ዛሬ ሲሉ ጠየቁ። ሴቶቹም ያጋጠማቸውን ይነግሯቸዋል። አባታቸውም ስማቸው ነብዩላህ ሹአይብ(አሰ) ይባላሉ። ደስ አላቸው ከዛም ጠርተው ሊያመሰግኑት እሺ ካለ ደግሞ ለሰራው ስራ ሊከፍሉት እንድትጠራው ከሁለቱ ልጆች መሀል ልቧ ጠብ ያለውን ልጅ ላኳት። እሳቸውም መች አወቁና። እየሮጠች ሄደች። ዛፍ ስር ቁጭ ብሎ አገኘችው። አይኗን ሰበር አርጋ አባቷ እንደሚፈልጉት ነገረቻቸው። ሙሳም (አሰ) ጥሪ ማክበር ዋጂብ ነውና እሺ አሉ። እሳቸው ከፊት እሷ ከሗላ ሆነው መንገዱን እሳቸው አያውቁትምና መታጠፍ ሲኖርባቸው በድምፅ ሳይሆን መታጠፍ ወዳለባቸው አቅጣጫ ጠጠር እየወረወረች እየመራቻቸው ከፊትና ተጠባብቀው አባቷ ቤት ገቡ። ልጅቷ በሰውዬው አላህን መፍራት፣ ታማኝነት አይናፋርነትና ጀንትልነት ይባስ ማረካት። አባትየውም ተቀበሉት። አመሰገኑት። ከየት ነህ አሉት። ታሪኩን ሙሉ ነገራቸው። አላህ አትርፎሀል አይዞህ ሲሉ አፅናኑት። ሙሳም መቼስ መንገደኛ ነውና ዛሬን አድሮ ነገ ወደማያውቀው መንገድ መጓዙ አይ