15/09/2025
የ2018 ትምህርት ዘመን ሰኞ መስከረም 05 ቀን 2018 ዓ/ም እንደሚጀመር ይታወቃል፡፡
በዲጂታል ዘመን በተማሪ ህይወት ላይ ትልቅ ተፅእኖ ከሚያሳድረው አንዱ ማህበራዊ ሚድያ ሲሆን እንደ ፦
- ቲክቶክ
- ኢንስታግራም
- ፌስቡክ
- X
- ቴሌግራም እና መሰል መተግበሪያዎችን ያለ አግባብ መጠቀም ትኩረትን ይቀንሳል ፣ የአካዳሚክ አፈጻጸምን ያዳክማል ፣ ጭንቀትና መሰል አሉታዊ የሆኑ ውጤቶችን ያመጣል።
ተማሪዎች ማህበራዊ ሚድያን ያለ አግባብ ሲጠቀሙ የሚገጥሟቸው ዋና ዋና ፈተናዎች ምንድን ናቸው ?
➡️ በኦንላይን የሚጠፋው ከልክ ያለፈ ጊዜ የተማሪዎችን ትኩረት እና ምርታማነትን ስለሚቀንስ ተማሪዎችን ወደ ደካማ የአካዳሚክ አፈፃፀም ያመራል፡፡
➡️ ከፍተኛ መጠን ያለው የስክሪን ጊዜ በተማሪዎች ላይ የስነ ልቦና ጫናን ያስከትላል።
➡️ በምሽት ማህበራዊ ሚዲያን አብዝቶ መጠቀም እንቅልፍ ለመተኛት እና ጤናማ እረፍትን ለማድረግ ከባድ ስለሚሆን የማስታወስ ችግርን ያስከትላል እንዲሁም የመማር ችሎታን ይቀንሳል፡፡
➡️ በማህበራዊ ሚዲያ ላይ የአካባቢ እና የትምህርት ቤት ስሞችን ወይም ስልክ ቁጥሮች እና መሰል የግል መረጃዎችን ማጋራት ለመጭበርበር እና ለሳይበር ጥቃት በቀላሉ ተጋላጭ ያደርጋል።
ተማሪዎች አዲሱን የትምህርት ዘመን ሲጀምሩ ማህበራዊ ሚዲያን አግባብ ባለው መልክ እንዲጠቀሙ መውሰድ ያለባቸው መፍትሄዎች ምንድን ናቸው ?
📇 የስክሪን ጊዜን መገደብ እና ማህበራዊ ሚዲያን ከመጠቀማቸው በፊት ለትምህርት ቤት ስራ ቅድሚያ በመስጠት ትኩረትን የሚከፋፍሉ ነገሮችን መቀነስ።
📇 ማህበራዊ ሚዲያን እንደ መዝናኛ ብቻ ከመመልከት ይልቅ የትምህርት መሳሪያ በማድረግ የጥናት ቡድኖችን በመቀላቀል፣ የአካዳሚክ ገጾችን በመከተልና አዳዲስ ክህሎቶችን በመማር የትምህርት ጊዜን የተሳካ ማድረግ።
📇 ከቤተሰብ ጋር ጊዜ ማሳለፍ ፣ መጽሐፍ ማንበብ ወይም የስፖርት እንቅስቃሴን በማድረግ የተሻለ ማህበራዊ ህይወት ልምምድ ማዳበር።
#ማስታወሻ ፦ ትምህርት ሚኒስቴር መስከረም 05/2018 ዓ/ም ከሚጀምረው የትምህርት ዘመን ጋር በተያያዘ ተማሪዎች ስልክን ጨምሮ ማንኛውም አይነት ኤሌክትሮኒክስ ቁሶችን ወደ ትምህርት ቤት ይዘው መምጣት እንደማይችሉ አስጠንቅቋል።
የማህበራዊ ድህረገጾቻችን ተከታይ ይሁኑ!!!
📘 Facebook: https://web.facebook.com/abacus.ethiopia
📸 TikTok: https://www.tiktok.com/
🔉Youtube: https://www.youtube.com/-abacus
💬 Join our parent community: https://t.me/Master_Abacus