20/08/2021
ስዖል ወይም ገሃነመ እሳት አለ ወይስ የለም?
አንዳንድ ሰዎች የሃይማኖትን ሰዎችን ጨምሮ ስለ ገሃነመ እሳት ያላቸው ግንዛቤ በጣም ያነሰ ሲሆን አንዳንዶች ደግሞ ፈፅሞ ምንም የማያወቁና ለማወቅም ምንም ፍላጎትና መነሳሳት የሌላቸው ናቸው::
ሆኖም ገሃነመ እሳት እግዚአብሔር ለሰይጣንና ለወደቁ መለኣክት በኃጢአታቸው ምክንያት የተዘጋጀ የቅጣት ቦታ እንደሆነ መጽሐፍ ቅዱስ ይናገራል:: እንዲሁ ሰዎችም በኋላ ላይ ሰይጣንን በመስማት ከእግዚአብሔር ዓላማ ውጭ በመሆናቸው ምክንያት በዚሁ ለሰይጣን በተዘጋጀው ስፍራ በገሃነመ እሳት በኃጢአታቸው ምክንያት እንደሚጣሉና ለዘላለም በሲቃይ እንደሚኖሩ ቃሉ ይናገራል::
የትኛውም ሰው የተማረ ያልተማረ ትንሽ ትልቅ ሳይል ሁሉም ኃጢአተኛ ነው :: በራሱ ጻድቅ ሰው የለም :: ሁሉም የእግዚአብሔር ክብር ጎድሎታል::
ስለዚህም ሰው ወደ እግዚአብሔር ክብር ለመመለስ የሚችለው ; ለኃጢአቱ ይቅርታ የሚያገኘው ; ከሲዖል አሰቃቂ ጥፋት መዳን የሚችለው; ከእግዚአብሔር ጋር በክብር በመንግሥቱ ውስጥ ከእርሱ ጋር መኖር የሚችለው; የዘላለም ሕይወት ሊኖረው የሚችለው ከዘላለም ጥፋት መዳን የሚችለው
በሚከተለው የሃይማኖት ስም ወይም ሥርአት ሳይሆን ስለ ሁሉም ወይም ስለ ኃጢአተኞች ሰለ አንተ ሰለአንቺ ሰለ እኔ ሰለ ሁላችንም ኃጢአት በመስቀል ላይ በሞተልን በኢየሱስ ክርስቶስ በማመን ወይም እንደገና ወይም ሁለተኛ በመወለድ ነው :: ይህን ቃሉ አስረግጦ ይነግረናል ይህን በናደርግ ግን የሚጠብቀን ሲዖልና ጥፋት ይጠብቀናል:: ወንድሜና እህቴ ሆይ አስብበት ዛሬ አቅልለህ ያየኸው ጉዳይ ነገ በሕይወትህ ላይ ሲሆን ስፍራ ባለመስጠትህ ምክንያት ቁጭትንና ጥፋትን ያመጣብሃልና ነገር ግን ትክረት ብትሰጠውና ነገሩን ብትመረምረው ከጥፋት የምታመልጥበትን መሠ ረታዊ ጉዳይ ታገኛለህና ተጠቃሚ ትሆናለህ:;
ከዚህ በታች የምታየው የእሳተ ገሞራ ደንጋይ ቀልጦ ፈሳሽ እሳት ነው::ስለሆነም ሲዖል ማለት ኃጢአተኞች ወይም በጌታ በማመን ዳግም ያልተወለዱ ወይም ኢየሱስን እንደ ግል አዳኛቸው ያልተቀበሉ ሰዎች ሁሉ የሚጣሉበት የእሳት ባህር ነው :: መ.ቅዱስ ትሉ የማይሞት እሳቱ የማይጠፋ እንደተባለ የሆነው ነው:: ስለዚህ የሲዖል መኖር እውነተኛ ነው የፍርዱ ሰዓት ደርሷልና ሳታመቻምች በጊዜ አምልጥ ብየ እመክርሃለው::
ይህንን ያልከህ ስለምወድህ እንጂ በከንቱ ጉዳይ ላጠምድህ እንዳልሆነ በትክክል ተረዳ::ለዚህ ደግሞ መጽሐፍ ቅዱስን አንብብ በግብዝነት አትመልከት በየትኛውም ምክንያት አትመካ ወደዚህ ምድር በራስህ ይዘኸው የመጣህ የእኔ የምትለው ምንም ነገር የለም ይዘህም የ ምትሄደው ነገር የለም:; በራስህ ማስተዋል አትደገፍ ቃሉን ስማ እርሱንም ተከተል እንጂ የጥፋትን መንገድ አትከተል:;
እግዚአብሔር በነገር ሁሉ ማሰተዋልን ይስጥህ::
እግዚአብሔር ዘመንህን ይባርክ!!!