Omo Union

Omo Union Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Omo Union, Baby & children's clothing store, Arba Minch'.

29/07/2025

14.8K likes, 535 comments. “ ”

28/08/2020

| ዶ/ር እንድሪያስ ጌታ የወላይታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ በመሆን ተሾሙ።
______________________________________
የወላይታ ዞን ምክር ቤት ለዛሬ በጠራው አስቸኳይ ጉባኤ ዶ/ር እንድሪያስ ጌታን የወላይታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ በማድረግ ሹሟል።

ምክርቤቱ ካሉት 114 አባላት መካከል 100 የሚሆኑት እንደተገኙበት በተገለጸው በዚህ አስቸኳይ ጉባኤ በቅርቡ ከሃላፊነት በተነሱት አቶ ዳጋቶ ኩምቤ ምትክ የአዲሱን ዋና አስተዳዳሪ ሹመት በአብላጫ ድምጽ አጽድቆታል።

ዶ/ር እንድሪያስ ጌታ እስካዛሬው ሹመት ድረስ የደቡብ ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር በመሆን ሲያገለግሉ መቆየታቸውን ጂ ኤም ኤን ከግለ-ታሪካቸው ለማወቅ ችሏል።

ከዚህ ቀደምም የወላይታ ሶዶ ግብና ኮሌጅ ዲን ሆነው አገልግለዋል።
አዲሱ ዋና አስተዳዳሪ ሹመቱን ከተቀበሉ በኋላ ባሰሙት ንግግር አስተዳደራቸው የዞኑን ሠላም ወደቀደመ ስፍራው ለመመለስ እና አስተማማኝ ለማድረግ የቅድሚያ ቅድሚያ ሰጥቶ ይሰራል ብለዋል።

የወላይታ ህዝብ የክልልነት ጥያቄን ከዞኑ ህዝብ ጋር በመመካከር በሠላማዊ መንገድ ብቻ ምላሽ እንዲያገኝ እንደሚሰሩም ተናግረዋል። “የለውጡ መንግስት የክልልነት ጥያቄን በአጭር ጊዜ ውስጥ ምላሽ እንደሚሰጥበት አልጠራጠርም” ያሉት ዶ/ር እንድሪያስ በቅርቡ በዞኑ በተከሰተው አለመረጋጋት በጠፋው የሰው ህይወት ማዘናቸውንም ገልፀዋል።

ከሠላም እና ፀጥታ መደፍረስ ጋር ተያይዞ የተቀዛቀዘው የዞኑ ኢኮኖሚ እንድያንሰራራ ይሰራል ያሉት ዋና አስተዳዳሪው ወላይታ ሶዶ ከተማን በመጪው 10 ዓመት ውስጥ የአፍሪካ ተመራጭ የቱሪዝም ከተማ ለማድረግ እሰራለሁ ሲሉም ተደምጠዋል።

21/08/2020
18/08/2020

በወላይታ ክልል እንሁን ጥያቄ እውን የወላይታ ህዝብ ተጠቃሚ ይሆናል?
➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫
ወላይታ ደቡብ ከሚገኙ ዞኖች በርካታ የህዝብ ቁጥር ካላቸው የሚመደብ ቢሆንም በቆዳ ስፋት ትንሹ ዞን ነው።

አንድ አከባቢ በክልል ደረጃ ይተዳደር ከተባለ በውስጡ ዞኖች ማደራጀት አስፈላጊ ስለሚሆን ለምሳሌ በወላይታ አረካን፣ ሁምቦን፣ ቦዲቲን እና ሶዶን ዞን ለማድረግ ቢታሰብ ተጠቃሚ የሚሆነው የወላይታ ህዝብ ሳይሆን ጥቅት ግለሰቦች ይሆናሉ።

ለዚህም ማሳያ የሚሆነው ለአንድ አከባቢ በጀት የሚበጀተው የህዝብ ቁጥርን መሠረት አድርጎ ስለሆነ ይህ ክልል እና ዞኖች የሚፈቀዱ ከሆነ ለልማት የሚውለው ለዞን መዋቅር ቢሮ ግምባታ እና ለጥቂት ተሿም ሠራተኛ ቅጥር እንኳን አይበቃም።

ከፌደራል ለክልል ድጎማ የሚሰጠው ክልሉ ለፌዴራሉ ከሚያስገኘው ገቢ መሠረት ተደርጎ ስለምሆን ከመጀመሪያው በወላይታ ነጋዴዎች ግብር ጫና ያስከትላል።

መንግስታዊ ካልሆኑ አካላት ገንዘብ ይገኛል ተብሎ ብታሰብም እንኳን ተስፋው የጨለመ ነው። ምክንያቱም የወላይታ ፖለቲከኞች ፊታቸውን ከለውጡ መሪ ወደ ህዋሃት እና የኦነግ ሼኔ ጋር ስላዞሮ።

#ለወላይታ ህዝብ ልማት ክልል ከመሆን ልዩ ዞን ቢሆኑ ያዋጣል። መነሻ ሀሳብ ነው በሀሳብ ሞግቱ።

ከቀጠናው ጋር ያለውን ግንኘነት....??
ለሟች ወገኖች መጽናናትን እመኛለሁ!

09/08/2020


!
የወላይታ ህዝብ የምክር ቤትና የካቢኔ አባላት እንዲሁም የብሄሩ ተወላጅ ሆነዉ በተለያዩ በክልሉም ሆነ በፌዴራል ደረጃ የሚገኙ የመንግስት የስራ ሐላፊወች የህዝባቸዉን ድምፅ በማስተጋባቸዉ ብቻ ያለምንም ወንጀል ከፊተኛ የማዋከብና የሰብዓዊ መብት ጥሰት አልፎም የጅምላ እስርዐእየተፈጸመባቸዉ ይገኛል። ይህንን ድርጊት የጋሞ ወጣቶች ማህበር ናቶ በፅኑ ይኮንናል ያወግዛልም። የጋሞ ተወካዮችም ከነዝህ ትጉህ አመራሮች ልምድ በመቅሰም ለህዝቡ ሁለኝተናዉ ተጠቃሚነት እንዲታገሉ ጥርያችንን እናቀርባለን።የአፈናና ዉድመት እንዲሁም የጅምላ እስር አካሄድ ባለፉት 27 ዓመታት እንዳየነዉ ለማንም ጥቅም የሌለዉ የዝንጆሮ ጉዞ መሆኑን በመረዳት መንግስት ከጀመረዉ የኋላ ማርሽ ጉዞዉን በመተዉ የዲሞክራሲ ምህዳሩን እንዲያሰፋ ጥርያችንን እናስተላልፋለን።

!!!
!!
!!

09/08/2020

|የወላይታ ዞን ከፍተኛ አመራሮች በቁጥጥር ሥር ዋሉ።
__________________________________________
የወላይታ ዞን ዋና አስተዳዳሪን ጨምሮ የብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት ሃላፊ እንዲሁም አጠቃላይ የዞኑ ሥራ አስፈጻሚ አባላት አመሻሹን በቁጥጥር ሥር መዋላቸው ታውቋል።

አመራሮቹ በቁጥጥር ሥር የዋሉት እሁድ ከሰዓት ከዞኑ የሀገር ሽማግሌዎች እና አክቲቪስቶች ጋር እየተወያዩ በነበሩበት የመሰብሰቢያ አዳራሽ መሆኑ ተገልጿል። ከአመራሮቹ በተጨማሪም ሌሎቹም አብረዋቸው ስብሰባውን የታደሙ ተሳታፊዎች በጠቅላላው 26 ግለሰቦች በፀጥታ አካላት ተይዘው ወደማረፍያ መወሰዳቸውን ጂ ኤም ኤን ለመስማት ችሏል።

የአመራሮቹን በቁጥጥር ሥር መዋልን ተከትሎ በዋና ከተማዋ ሶዶ አለመረጋጋት ተከስቷል። የክልሉ ልዩ ሀይል እና መከላከያ እንዲሁም ሌሎች የፀጥታ ሀይሎች የተቀሰቀሰውን ሁከት ለማብረድ እየሞከሩ ስለመሆኑ ተነግሯል።

ጂ ኤም ኤን ሶዶ ከሚገኝ ወኪሉ ያገኘው መረጃ እንደሚያሳየው በከተማዋ ላለፉት ጥቂት ሰዓታት ከባድ የቶክስ ድምጽ ሲሰማ ቆይቷል። በተጨማሪም ለተቃውሞ አደባባይ በወጡ ነዋሪዎች እና የጸጥታ ሀይሉ መካከል ግጭት ተፈጥሯል።

ይህ በእንዲህ እንዳለ የደቡብ ክልል ሠላም እና ፀጥታ አስተዳደር መመሪያ ሀላፊ አቶ አለማየሁ ባውዱ እንዲሁም የክልሉ ፖሊስ ኮምሽን ኮምሽነር ሁኔታውን አስመልክቶ አመሻሹ ላይ በሰጡት መግለጫ በቁጥጥር ሥር የዋሉት አመራሮች የወላይታን ህዝብ ከሌሎች የአጎራባች ዞኖች ህዝቦች ጋር ለማጋጨት ብሎም በዞኑ ውስጥ ሁከት ለማስነሳት ከህወሓት እና ኦነግ ሸኔ ጋር ሲሰሩ ነበር በማለት ገልፀዋል። በተለይም የዞኑ ሥራ አስፈፃሚ ከዚህን በፊት በጉዳዩ ላይ የተሰጠውን ተደጋጋሚ ማስጠንቀቂያ ችላ በማለት በዛሬው ዕለት ከወላይታ የክልል አደረጃጀት ጥያቄ ጋር በተያያዘ ክልሉን ወደሁከት መቀየር በሚቻልባቸው ጉዳዮች ዙሪያ ለመምከር ከኮማንድ ፖስት ዕውቅና ውጪ የሆነ ህገወጥ ስብሰባ በማድረግ ላይ እንዳሉ በህግ ቁጥጥር ሥር ሊውሉ ችለዋል።የዞኑ ከፍተኛ አመራር ከህወሓት-ኦነግ ሸኔ ጋር በትብብር ሲሰራ እንደቆየ የደቡብ ክልል መንግስት ሠላም እና ፀጥታ አስተዳደር መምሪያ ከብሄራዊ የመረጃ ደህንነት ኤጄንሲ ጋር በመሆን ባከናወነው ምርመራ ማረጋገጡን ሀላፊዎቹ በመግለጫቸው ላይ አስታውቀዋል።

ዛሬ በቁጥጥር ሥር የዋሉት ከፍተኛ አመራሮችን ጨምሮ በጠቅላላው 26 ተጠርጣሪዎች በቅርቡ ክስ ተመስርቶባቸው ለፍርድ እንደሚቀርቡም የደቡብ ክልል መንግስት ሠላም እና ፀጥታ አስተዳደር መምሪያ ሀላፊ አቶ አለማየሁ ባውዲ በሰጡት መግለጫ ተናግረዋል። በሀዋሳ ከተማ እየተካሄደ በሚገኘው የደቡብ ክልል ም/ቤት ጉባኤ የወላይታ ዞን ተወካዮች እና አመራሮች ክልል ለመሆን ያቀረብነው ጥያቄ እስካልተመለሰ ድረስ አንካፈልም በሚል መቅረታቸው ይታወቃል።

16/06/2020

#በኢትዮጵያ የመጀመሪያው ሲኖግራፊ ምርመራ መሳሪያ አርባምንጭ ሆስፒታል ነበር።
በ1977 ነበር አገልግሎት መስጠት የጀመረው። በ60ዎቹና 70ዎቹ እንዲሁም በ80ዎቹ መጀመሪያ የአርባምንጭ ሆስፒታል በብዙ አገልግሎቶች
በኢትዮጵያ ተመራጭ ነበር።
ከአዲስ አበባና አስመራ ታካሚዎች ይመጡ ነበር።
ስንቶቻችን እንሆን ይህንን የምናውቀው?
መረጃውንና ፎቶውን የላከልንን Leul Dawit እናመሰግናለን

14/06/2020

#ሰበር ዜና
#ኦሞቲክ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የማይቀር ጉዳይ ነው፡፡
★★★★★★★★★★★★★★★★★
ከመጀመሪያው ውይይት ስነሳ ቀደም ሲል በዶ/ር አብይ አሕመድ አማካኝነት የደቡብ ክልል አድሱ አዴሬጃጀት ላይ ለመምከር አስተዳዳሪዎች፣ ብልፅግና ጽ/ቤት ሀላፍዎች እና ዋና አፌ ጉባኤዎችን በጠቅላይ ሚንስተር ጽ/ቤት መወያዬታቸው ይታወቃል፡፡
የጋሞ ዞን እና የጎፋ ዞን ተወካዮችን ውይይቱ ከመካሄዱ በፍት ከተስፋዬ በልጂገ እና ከጥላሁን ከበዴ ጋር ሀሳቡን የጋራ ለማድሬግ መምከራቸውን ሳይስማሙ መለያዬታቸውን አሬጋግጠናል፡፡
በዚህ ምክክር ወቅት ከአቶ ተስፋዬ በልጂገ እና ከአቶ ጥላሁን ከበዴ የተነሱ ሀሳቦች ጋሞ፣ ወላይታ፣ ጎፋ፣ ባስከቶ፣ ኮሬ፣ ድራሼ፣ ኮንሶ እና ደቡብ ኦሞ ጨምሮ በኦሞቲክ ክልል እንድዋቀር 99% ያሬጋገጥን ስለሆኔ በምቀርበው አዴሬጃጀት ላይ አሉታዊ የሆኔ አስተያዬት እንዳትሰጡ የምል ምክር አዜል ማስጠንቀቅያ የሰጡ መሆኑን ልናሬጋግጥ ችለናል፡፡
በዚህ ምክር ሀሳብ የጋሞ ተወካዮች ሀሳባቸውን ስያንፀባርቁ፦ ቀድሞ እድሉን ያገኘው አቶ ማሄ ቦዳ እንደዚህ ዓይነት ከህዝብ ፍላጎት ጋር የምያጋጭ ሀሳብ ተሸክሜን ወዴ ስብሰባው እኔ በበኩሌ ልገባ አልችልም ሲል ውግንናውን ገልፆዋል፡፡ አክለውም እንደገለፀው የጋሞ ህዝብ ጥያቄ በመጀመሪያ ደሬጃ የጋሞ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ሲሆን ይህ የማይሆን ከሆኔ አርባምንጭን ማዕከል ያደሬገ ወላይታ ዞንን ያላካቴቴ ከሀማሳ ወንዝ እስከ ቱርካንያ ሀይቅ ድሬስ እንድሰጥ፤ ይህ የማይሆን ከሆኔ የሰጣችሁትን ሥልጣን ከዛሬ ጀምሮ መውሰድ እንደምትችሉ ላሬጋግጣችሁ እወዳለው ሲል አስበርግጋቸዋል፡፡
አቶ ብርሃኑ ዜውዴን ጨምሮ ዋና አፌ ጉባኤዋ ይህንን አቋም የጋራ በማድሬግ ወዴ ቀጣይ ስብሰባ አዴራሽ አቅንተዋል፡፡ ስብሰባውን የዞን አመራሮች በአቋም መወጣታቸውን እንድሁም የጎፋ ዞን አስተዳደር ከወላይታ ጋር እንኳን በምድር በሰማይም አንሆንም ሲል የጎፋ ህዝብ አቋም መግለፁንና የወላይታ አመራሮች አንገት ማስደፋቱን አሬጋግጤናል፡፡
የኦሞቲክ ክልል አቀንቃኝ የሆነው የቀድሞ ጠቅላይ ሚንስተር አቶ ሀይለማሪያም ደሳለኝ በተለያዩ ውለታዎች የዶ/ር አብይ አሕመድን አቅም እያሽመደመደ ይገኛል፡፡ የጋሞም የወላይታም ህዝብ በማይፈልግበት መልኩ፤ ዶ/ር አብይ አሕመድ ሳያምንቤት በይሉንታ ብቻ የአንድ የከሰሬ ፖለቲከኛ ሞራል ለመጠበቅ ሲል ብቻ ኦሞቲክ ክልል ለማዋቀር ጫፍ የደሬሱ መሆኑን አሬጋግጠናል፡፡
በዚህ አደሬጃጀት ጋሞ ህዝብን ብሎም የጋሞ ምሁራንን እንዴት ማሳመኔ ይቻላል ለተባለው ጥያቄ አስፈላጊውን ዕቅድ መታቀዱ ተሬጋግጦዋል፡፡
በመጀመርያ ደሬጃ የጋሞ ዞን አመራሮች አቋማቸውን እንድያስተካክሉ አቅጣጣ ተቀምጦ እርምት እርምጃ ተወስዶባቸዋል፡፡
ዋኔኛው ዕቅድ ጋሞ ዴሞክራሲ ፓርቲ ላይ በጎ ተፅኖ በመፍጠር ወላይታን ያካቴቴ ኦሞቲክ ክልል ማዋቀር ነው፡፡ ፡
የጋሞ ሠላም ተምሳሌትነት እና አቃፍነትን በመጠቀም የጋሞ ማማክርት እና የጋሞ ሀገር ሽማግሌዎች የካቴቴ ፋናል ውይይት በማካሄድ ወላይታን ያካቴት ኦሞቲክን ክልል በማደራጀት ህዝቡ ሳይወድ በግድ ማሳመን በጎ ተፅኖ መፍጠር ዋነኛው ነው፡፡
ይህን አዴሬጃጀት ለማሳካት በዶ/ር አብይ አሕመድ ሰብሳብነት የጋሞ ተፅኖ ፈጣሪ የምባሉ ምሁራንን በቅርቡ የማግባባት ሥራ ይከናወናል፡፡
ከዚያም ይህን የማግባባት ሥራ ይከናወንና በጋራ መግባባት የአስተዳደር ጨምሮ በርካታ ማዕከላት ይከፋፈላሉ፡፡ ይህም ተፌፃም ይሆናል፡፡
ይህ አዴሬጃጀት በበላይኔት በአቶ ጥላሁን ከበዴ ርዕሴ መስተዳደርነት ይመራል፡፡ ይህም ቃል ተገብቶለት አቅሙን አሟጦ እየሰራ ይገኛል፡፡

Address

Arba Minch'

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Omo Union posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share