19/07/2026
ገበሬው እርሻው ላይ እያለ፣ አንዲት ሚዳቋ በከፍተኛ ፍጥነት እየሮጠች መጣችና ሳታስተውል እዚያው እርሻ ውስጥ ከነበረ የዛፍ ጉቶ ጋር ተጋጭታ አንገቷ ተሰብሮ ሞተች።..
ገበሬውም ያለምንም ድካም ያገኛትን ሚዳቋ ወስዶ አርዶ በላት። በዚህም በጣም ተደሰተ። ከዚያን ቀን ጀምሮ ገበሬው "ታዲያ በየቀኑ በፀሐይና በብርድ እየደከምኩ ለምን እታገላለሁ? በየቀኑ እዚህ ዛፍ ሥር ቁጭ ብዬ ሚዳቋ እስክትመጣልኝ መጠበቅ እችላለሁ እኮ!" ብሎ አሰበ።..
እርሻ ማረሱንና መኮትኮቱን ትቶ፣ በየቀኑ ከዛፉ ጉቶ አጠገብ ቁጭ ብሎ ሌላ ሚዳቋ እስክትመጣና እስክትጋጭለት መጠበቅ ጀመረ። ቀናት፣ ሳምንታትና ወራት አለፉ፤ ነገር ግን ሌላ ሚዳቋ ፈጽሞ አልመጣችም። በመጨረሻም እርሻው በሳርና በአረም ተሸፈነ፤ ምንም እህል ማምረት አልቻለም። ገበሬውም በሰነፍ አስተሳሰቡና በአቋራጭ ለመክበር በመመኘቱ ምክንያት ለረሃብና ለችግር ተዳረገ። በመጨረሻም እንዲህ አለ "ነፃ ምሳ ብሎ ነገር የለም።" There is no free lunch እንደማለት። ..
እዚህ ዓለም ላይ ነፃ ብሎ ነገር የለም፤ በነፃ አትታገዝም፤ በነፃ ብር አይገኝም፤ በነፃ ጥበብ የለም። ሁሉም ነገር ልፋት እና ጥረት ይፈልጋል።
https://OmoUnion.com